Monday, November 27, 2017

የአማራ ሴቶች ማህበር የከተማ አባላት በተለያዩ የጥቃቅን የስራ ዘርፎች ተሰማርተዉ ተጠቃሚነታቸዉን ለማጎልበት የይሰራል

የአማራ ሴቶች ማህበር የከተማ አባላት በተለያዩ የጥቃቅን የስራ ዘርፎች ተሰማርተዉ ተጠቃሚነታቸዉን ለማጎልበት ከተለያዩ የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት ጋር በመቀናጀት በርካታ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱ ይታወቃል፡፡አባላት በተለያዩ የስራ ዘርፎች (በማገዶ ቆጣቢ ምድጃ፣ በባልትና ዉጤቶች፣ በልዩ ልዩ የግንባታ ዕቃ ማምረት፣ በከተማ ግብርና፣ በአገልግሎት ወ.ዘ.ተ) እንዲሰማሩ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ታቅዶ 7‚286 አባላትን  ወደስራ ማስገባት ተችሏል፡፡ 




በተለይም የጥቃቅን ዘርፍ ስራዎች መነሻ ካፒታል የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ማህበሩ በሁሉም መዋቅሩ አባላት ከህብረት ስራ ማህበራት፣ከአብቁተና ሌሎችም አበዳሪ ተቋማት ብድር አግኝተው ወደ ስራ እንዲገቡ በማድረግ  አባላት ያለባቸውን የመስሪያ ገንዘብ (የመነሻ ካፒታል) እጥረት ለመፍታት ጥረት ያደርጋል፡፡ በዚህም ባሳለፍናቸው ሶስት ወራት 6‚961አባላት 1‚271‚600 ብር ብድር እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ 
 አባላት ወደ ስራ የሚያስገባ ብድር ከአበዳሪ ተቋማት እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ የሚያገኙትን ብድርም ለተባለለት አላማ እንዲያውሉትና በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ከቢዝነስ ፕላንና ስራ አመራር ስልጠና ጀምሮ በመስጠት ውጤታማ ሆነው ነገ ወደ ዘርፉ ለሚገቡ ሴቶች አርአያ ሆነው የተሞክሮ ማሳያ እንዲሆኑ ሙሉና ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ይህን ስራ ሲሰራም ከሚመለከታቸው ተቋማት የሚደረግለት ሙያዊ ድጋፍና ትብብር ማህበሩ ሁሌም ብርታት እንዲሰማው የሚያደርግ በመሆኑ መላው አጋሮቻችን ልናመሰግን እንወዳለን፡፡

Tuesday, July 25, 2017

ሄሊንግ ሀንድስ ኦፍ ጆይተጋልጠው ህክምና የተደረገላቸው እናቶችን በህይወት ክህሎት፣በስራ ፈጠራና በጤናማ እናትነት ዙሪያ አሰልጥኖ አስመረቀ፡፡



ሄሊንግ ሀንድስ ኦፍ ጆይ የተባለው ግብረ ሰናይ ድርጅት ለፌስቱላ ተጋልጠው ህክምና የተደረገላቸው  እናቶችን በህይወት ክህሎት፣በስራ ፈጠራና በጤናማ እናትነት ዙሪያ አሰልጥኖ አስመረቀ፡፡ድርጅቱ በዚህ ዘርፍ ከአማራ ሴቶች ማህበር ጋር በአጋርነት ይሰራል፡፡
የህክምና ባለሞያዎች እንደሚገልፁት በሽንት ፊኛና በማሕፀን መካከል የሚፈጠር ቀድሞ ያልነበረ ቀዳዳ ፌስቱላ ይባላል፡፡ ዋና ምክንያቱ ካለእድሜ ጋብቻ፣በወሊድ ወቅት በጤና ተቋም ባለመውለድ በሚያጋጥም የተራዘመ ምጥ አልፎ አልፎም በመውደቅ ፣በህክምና ስህተትና በበርካታ ሌሎች ምክንያቶች  ሴቶች ለዚህ ችግር ሲጋለጡ  በሽታው በሚፈጥረው ሽታ ምክንያት  ከማህበረሰቡ የመገለል፣ ለፍችና አካላቸው በእንቅስቃሴ እጥረት የመተሳሰር ችግሮች ይዳረጋሉ፡፡
 ይህን ለውስብስብ የጤና እክሎች የሚዳርግ በሽታ ህክምና በ 1959 በዶክተር ካትሪን ሀምሊን ተጀምሮ የበርካታ ሴቶችን ህይወት ከአካላዊና ከስነ-ልቦና ቀውስ መታደግ ከተጀመረ 50 አመታት ቢቆጠሩም ከህክምናው ባለፈ ሴቶች ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ ምን ይገጥማቸዋል፣ምንስ ይሰራሉ፣የስነ-ልቦና ጉዳታቸው እንዴት ይጠገናል የሚሉት ጥያቄዎች መልስ አልባ ስለነበሩ ሴቶች በሚደረግላቸው ህክምና ከአካላዊ ህመማቸው ቢፈወሱም አእምሯዊ ቁስላቸው ሳይፈወስ ስለሚቀር ወደ ቀያቸው ለመሄድ መቸገርና በከተማ የመቅረት፣የችግራቸው መንስኤ በማድረግ ወንድ የመጥላት፣ትዳራቸውን እንደፈቱ በፍርሃት ከጋብቻ መታቀብ፣ዳግም ላለመውለድ በመፍራት ፍች መጠየቅ የመሳሰሉ ውስብስብ  ችግሮች ይዳረጉ ስለነበር ይህን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል ስራ በመስራት ላይ የሚገኘው ሄሊንግ ሀንድስ ኦፍ ጆይ ሴቶችን ከህክምና በኋላ በመረከብ ህይወታቸውን በመሰረታዊነት ሊቀይሩባቸው የሚችሉ ስልጠናዎችን ከመስጠት ባለፈ በአማራ ሴቶች ማህበር አማካኝነት የሚፈፀም ከወለድ ነፃ የተዘዋዋሪ ብድር ገንዘብ በመልቀቅ ሴቶች የተሰጣቸውን ስልጠና መሰረት አድርገው ሰርተው እንዲለወጡና ቤተሰባቸውን በማስተዳደር አርአያ እንዲሆኑ በተለይም እነዚህ እናቶች በጤናማ እናትነት አምባሳደር በመሆን እናቶች በጤና ተቋም እንዲወልዱ በማስተማር እነሱን የገጠማቸው ችግር በሌሎች እንዳይደርስ ከማድረግ ባለፈ ለፌስቱላ ተጋልጠው በቤታቸው ተደብቀው የተቀመጡ ሴቶችን ወደ ህክምና ተቋሙ በማምጣት ህክምና እንዲያገኙ የሚያደርጉ የተቋሙ ሰንሰለቶች በማድረግ በየጊዜው እያስመረቀ ወደ ቀያቸው ይመልሳል፡፡
በዚህም በለጋ እድሜያቸው ሳቃቸው የጨለመና ከሰው ተራ ወጥተው ተስፋቸው በጠዋት የተነነ የመሰላቸው ሴቶችን የጠዋት ሳቃቸውን የመለሰ፣ወልዶ የመሳም ተስፋቸው በምን ሰርቼ ሳይጨነግፍ ሰርተው ከሰው ተራ የተሰለፉ በርካታ እናቶችን ለውጤት እያበቃ ይገኛል፡፡

Wednesday, April 12, 2017

ሴቶች የለውጥ ሀዋሪያት እንደሚሆኑም እርግጠኛ ነኝ ፡፡





 















የዛሬ ማንነቴን የቀረፀልኝ በገዳም ያሳለፍኩት ጊዜ ነው፡፡ በአደግኩበት በሀረር የካቶሊክ ገዳም በደስታ የተሞላ የልጅነት ጊዜ አሳልፌያለሁ፡፡ዛሬ የደረስኩበት ደረጃ ለመድረስ ያላለፍኩት እሾህና መሰናክ አልነበረም፡፡ያለወላጆቼ ድጋፍ በገዳም አድጌያለሁ፡፡ልታሳድገኝ የወሰደችኝ አክስቴ የቤት ሰራተኛና የል ሞግዚት አድርጋኝ ነበር፡፡ይህን በትግል  የተወጣሁት ህልም ስለነበረኝ ነው፡፡ ህልሜን እውን ለማድረግም ፈተናዎችን አሳልፌያለሁ፡፡ ዛሬ ግን እዚህ ነኝ፡፡ በህዝብ የሚጎርፍልኝ አድናቆት ምግቤ ነው፡፡ያደግኩት ያለቤተሰብ ፍቅር ነውና፡፡
ሴቶች አቅማቸው አልታየም ብየ አምናለሁ ፡፡ የህልማችን  ለመሆን አቅማችን አጠን እንጠቀም ፡፡ወደፊት የሴቶች ተሳትፎ እንደሚያድግና አገራችን ታላቅ እድገት እንደምታስመዘግብ ከልቤ አምናለሁ ሴቶች የለውጥ ሀዋሪያት እንደሚሆኑም እርግጠኛ  ነኝ ፡፡
ሙሉአለም ታደሰ  
ለተምሳሌት

Tuesday, April 11, 2017

ማኀበራት/ድርጅት ማለት ምን ማለት ነዉ? መደራጀትስ ?






ማኀበራት/ድርጅት ማለት ምን ማለት ነዉ?






  በማህበራዊ ሳይንስ የእንግሊዘኛ ትርጉም መሰረት ድርጅት/አደረጃጀት
“ organization is a highly organized group having explicit objectives, formally stated rules and regulations and a system of specifically defined roles, each with clearly designated rights and duties.”
ድርጅት/አደረጃጀት ግል ዓላማ፣በአግባቡ የተደነገገ ህግና መተዳደሪያ ደንብ ያለው፣እያንዳንዱ አባል በድርጅቱ/ማህበሩ ውስጥ የተወሰነና ግል የሆነ ሚና ፣በግል የተቀመጡ መብቶች፣ተግባርና ሃላፊነቶች ያሉት በስርአት የሚመራ በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ የሰዎች ስብስብ ነው፡፡
  ልዩ ልዩ  የህ/ሰብ  ክፍሎች  ተመሣሣይ  ፍላጎትና ጥቅማቸውን  ለማሣካት  ሲሉ  የአጭርና የረዥም ጊዜ ግባቸውን  በመለየትና ይህንን  ለማስፈፀም አቅጣጫዎች  በማስቀመጥና ድርጅቱን (ማኀበሩን )የሚያስተዳድሩበት  መርሆዎች የጋራ ደንቦች ቀርፀው የሚያቋቁሙት የጋራ ፍላጎታቸውና  ጥቅማቸውን ማስፈፀሚያ መሣሪያ ነው፡፡
  እንደየ አባላቱ የአደረጃጀት ፍላጐት ማህበራት በሚከተሉት አይነት  ሊቋቋሙ ይችላሉ፡፡ለምሣሌ -
ü  የብዙኃን ማህበራት / የሴቶች የወጣቶች የአርሶ አደሮች ወዘተ ማህበራት /
ü  የሙያ ማህበራት / የመምህራን  የጤና ባለሙያዎች   የህግ ባለሙያዎች   ማህበርወዘተ
ü    የህብረት ስራ ማህበራት / በገቢ ማስገኛ የተሰማሩ  የሸማ ሰሪዎች የባልትና ውጤቶች አቅራቢ ህብረት ስራ ማህበርወዘተ
ü እነዚህ  አደረጃጅቶች -
ü  ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ
ü    ለፈጣን  ልማት መረጋገጥ እንዲያስችል ሰፊውን ህዝብ በተደራጀ መልኩ በማንቀሣቀስ የልማት ቀጥታ ተሣታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ
ü  የአባላትን መብትና ጥቅም ለማስከበር የጐላ ሚና ስላላቸው በብዛትና በጥራት እንዲፈጠሩና እንዲጠናከሩ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ተገቢ ነው፡፡
ü  በግሎባላይዜሽን ዘመን መንግስት  ብቻውን ልማቱን በማካሄድ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት እና የዜጐቹን ፍላጎት ለማሟላት ይቻላል ብሎ ማሰብ ፈጽሞ የሚታሰብ አይደለም፡፡
ስለሆነም ከድህነት እሽክርክሪት ( poverty Cycle  ) ለመውጣት /ሰቡ በሚፈለገው የህዝብ አደረጃጀቶች እንዲደራጅ ማድረግ ተገቢ ነዉ፡፡
  • ሴቶች ከኢኮኖሚ ጥገኝነት ወጥተው የራሳቸው ሃብትና ንብረት እንዲያፈሩ

    በሙያቸው፣ ታቸውና በእድሜያቸው በሌሎችም በጋራ ሊሰሩባቸውና ሊታገሉባቸው በሚችሉበት አደረጃጀቶች ተደራጅተው  ያሉባቸውን መሰረታዊ ችግሮች ለመፍታት አስፈላጊ ናቸው፡፡
መደራጀት አስፈላጊ ነው ከምንልባቸው አሳማኝ  ምክንያቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ፤
  ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች በተደራጀ መልክ ለማስጠበቅና የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን ለማስከበር፣
   በህይወት የመኖር፣፣በአካሉ ግዳት እንዳይደርስበት የመጠበቅ ሃሳብን በነ የመግለ፣የመሰብሰብ የመምረጥ መመረጥ ወዘተ
  ሕገ መንግስታዊ መብትን ለማስከበር  / ሕገ. . አንቀፅ 31 ንዑስ .1 /  «ማንኛውም ሰው ለማንኛው ዓላማ በማህበር  የመደራጀት መብት ሰጥቷል»
  በየደረጃው ያሉ መንግስታዊ አካላት በሚያወጧቸው  ፖሊሲዎች መመሪያዎች ሕጐችና  ደንቦች የህብረተሰቡን ተሣታፊነትና ተጠቃሚነት ያካተቱና የሚያረጋግጡ ስለመሆናቸው አውንታዊ ተጽዕኖ  ለማሣረፍ
  በተናጠልና  በግል ሊፈቱ የማይችሉ ጉዳዩች በመተባበር መፍትሔ እንዲያገኙ  ለማድረግ
  በፆታ ምክንያት የሚፈጠሩ አድሉአዊ አሠራሮችንና በደሎችን እንዲወገዱ ለመታገል፣
  የሙያ ብቃትን ለማሣደግ ሙያን ለማስከበር፣
  እንዲሁም በሙያቸው የሚጠበቅባቸውን አስተዋ ለሀገር እንዲያበረክቱ
   ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስወገድና ጠቃሚ ባህሎችን በማጎልበት በኩል ጉልህ ሚና ለመጫዎት፣
   የማኀበረሰብ ንቅናቄ በተደራጀ መልኩ  በመፍጠር የሴቶችን ተሣታፊነትና ተጠቃሚነት ለማሣደግ፣
  ገንዘብ፣እውቀትንና ጉልበትን በጋራ አቀናጅቶ በመጠቀም ተጨባጭ ልማታዊ ለውጥ ለማምጣትና ከሚገኘው ጥቅም በቀጥታ ተጠቃሚ ለመሆን፣
  የጋራ ጉዳዮቻቸውን የሚመክሩበትና አቋም የሚወስዱባቸውን መድረኮች  ለመፍጠር፣
  በአካባቢ በሚካሄዱ  የልማት እንቅስቃሴዎች እና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ የተደራጀ አቅም በመፍጠር መሣተፍ እንዲቻልና ከሚገኘው ውጤትም ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ፣
  የተለያዩ ማህበራት መኖር ጠንካራና በመልካም አስተዳደር የተገነባ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲፈጠር አጋዥነታቸው የጐላ ስለሚሆን፣
  የሕብረተሰቡን  ተጠቃሚነትና ተሣታፊነት የሚያረጋግጡ ተጨማሪ አዳዲስ ፖሊሲዎች ሕጐች ደንቦች፣ መመሪያዎች እንዲወጡ ሀሣብ በማመንጨት በኩል አስተዋጽኦ  ለማድረግ፣
  ከመንግስትና የተለያዩ አካላት የተለያዩ የአቅም ግንባታ ድጋፎችን ለማግኘትወዘተ መደራጀት በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡